ኢጋድ ኢትዮጵያዊውን አማካሪ ከሥራ አሰናበተ
የምሥራቅ አፍሪካ ሃገሮች የጋራ ልማት ባለሥልጣን /ኢጋድ/ የተቋሙ ከፍተኛ አማካሪ የነበሩትን ኮሎኔል ገብረእግዚአብሄር ዓለምሰገድን አሰናብቷል።
በኢጋድ ዋና ፀሐፊ በአምባሳደር ማሕቡብ ሙአሊም የተፈረመ ደብዳቤ ባለሥልጣኑ የኮሎኔል ገብረእግዚአብሄር ዓለምሰገድን አገልግሎት ማቋረጡን ይናገራል።
ይህ ሰኞ፣ ሰኔ 18/2010 ዓ.ም. የተፃፈ ደብዳቤ ስለኮሎኔል ገብረእግዚአብሄር ዓለምሰገድ መሰናበት ዝርዝር አላሰፈረም። ይሁን እንጂ ሥራቸውን ያስቆማቸው በዚያኑ ቀን መሆኑን አስታውቆ የአደጋን ንብረት ሁሉ ከትናንት በስተያ ከቀኑ ስምንት ሰዓት ተኩል በፊት እንዲያስረክቡ አዝዟል።


Comments