Posts

Showing posts from March, 2018

አብይ ፍሬውን ለቀማ

ዘራቸውን ይተክላሉ አብይ ፍሬውን ለቀማ ነፋስ የገባው ገለባ ፍሬ አልባ ዋግ የበላው መሆኑን ወገን ሳይሰማ ምን አይንት መስገብገብ ነው ይሄ ነው እንዴ መሰረቱ ዘሩን በደንብ ሳይተክሉ በፍሬው ላይ መሟገቱ ውሃ ሳያዘጋጁ ፈሰሱን ሳይሸነሽኑ እርከኑን ሳይደለድሉ  የነገ ተስፋው ቀጭጮ መንምኖ እያያችሁት  ገና ከእንጭጩ ቁጭ ብሎ ከፍሬው ተመኛችሁት በሉ እንግዲህ እንየው የዘመናት ፉጨቱን  አራት ምሶሶ ተተክሎ መቆም ከተሳናችሁ ያው ለምስል ካልሆነ ምኑን kፌሬው በላችሁ፡፡

በዚህ ሰአት ኦሮሞ ሀገር የመምራት ብቃት እንዳለው የማሳየት ግዴታም እድልም አለው!

Image
በበዚህ ሰአት ኦሮሞ ሀገር የመምራት ብቃት እንዳለው የማሳየት ግዴታም እድልም አለው! ፕሬዘዳንትነቱን----ዶክተር ሙላቱ ተሸመ ጠቅላይ ሚኒስትረቱን--ዶክተር አብይ አህመድ አፈ ጉባኤነቱን አቶ አባዱላ ገመዳ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ይዘውታል ፡፡ የአመራር ብቃታቸውን እስኪ ልናይ ተቃረበናል ! እንህን ቁልፍ ቦታዎች ርዕሳነ ሀገር ተሸክሞ እንደ አሻንጉሊት ከተቀመጡ በማንነት ላይ ትልቅ ጥያቄ አለ ! ብዬ አምናለሁ!

አዲሱ የኦህዴድ ተወካይ ዶክተር አብይ ጠቅላይ ሚኒስተር መመረጣቸው እና የደመቀ መኮነን ከምርጫ እራሳቸውን የማግለል ጉዳይ ፖለቲካዊ አንድምታው፡፡

Image
አዲሱ የኦህዴድ ተወካይ ዶክተር አብይ ጠቅላይ ሚኒስተር መመረጣቸው እና የደመቀ መኮነን ከምርጫ እራሳቸውን የማግለል ጉዳይ ፖለቲካዊ አንድምታው፡፡ አቶ ሐይለማርያም ደሳለኝ ከስልጣን እራሰቸውን ካገለሉ ማግስት ኢትዮጵያችን ምጥ በሚመስል መልኩ ጠቅላይ ሚኒስተሯን ለመሾም ስትጨነቅ ሰንብታ አሁን እንደምንም ሰው እንቅልፍ በወሰደበት ከሌለቱ አምስት ሰኣት ላይ ይፋ ሆኗል ፡፡ እንደምናውቀው ከውጭም ሆነ አገር ውስጥ ያሉ የኦሮሞ ተቆርቋሪ ነን ባዮች ኦሮሞ አገር መርቷል የሚባለውን ታሪክ ስም ብቻ የፈለጉ እስኪመስል ድረስ ዶር አብይ………..ይ እያሉ ከወዲያም ከወዲህም ሲያስተጋቡ መክረማቸው ይታወቃል ፡፡ኢሀዴግም ይሄን ፍላጎታቸውን እውን አድርጎላቸዋል፡፡ እንደሚመስለኝ አቶ ደመቀ መኮነን እራሳቸውን የማግለሉ ጉዳይ ለመመረጥ በህገ መንግስቱ ላይ ታላቅ ድጋፍ የ ነበረው ምክትል የነበረው ደመቀ በመሆኑ ይሄንን ህግ ተከትለው ቢመርጡት የኦሮሞ ብሄርተኛች ሊፈጥሩት የሚችሉትን ተቃውሞ ከግምት ውስት በማስገባት ምክትሉ እራሱን እንዲያገል እና የኦሮሞዎችን ልብ እንደማብረጃነት ሊጠቀሙት በማሰብ የተቀነባበረ ይመስላል ምክንያቱም በዚህ የውጥረት ሰአት አቶ ደመቀ ቢመረጥ የኦሮሞ ብሄርተኞች ከእሳት ላይ ገለባ እንደመጨመር ስለሚመስላቸው የአማራው ብሄርተኞች የስርአት ለውጥን እንጅ በኢሀዴግ አጠራር ስር ነቀል ተሀድሶው ብዙም እንደማያስጨንቃቸው በመገንዘብ የግድ ዶክተር አብይ ወደ ጠቅላይ ሚኒስትርነት እንዲመጡ ተገደዱ ፡፡ ዋነው ቁምነገር ለአማራውያን ዶክተር አብይ መመሩጡ ወይም ደመቀ መመረጡ ትርጉም ያለው ፍሬ ነገር አይደለም ጉልቻ ቢቀየር ወጥ አያጣፍጥም በሚለው ብሂል ! ቁምነገሩ 1፡- ዶክተር አብይ የኦነግን እቅድ ለማሳካት ከነጃዋር ጋር ያለው ግልቢያ የጀርባ አጀንዳ ካደረጉና የ...

አይኗ በልጆቿ የታወረች ሀገር፣የሚጠቅሟት ልጆቿን መብላት የጀመረች ኢትዮጵያ!

አይኗ በልጆቿ የታወረች ሀገር፣የሚጠቅሟት ልጆቿን መብላት የጀመረች ኢትዮጵያ! ይህች ታሪካዊት ሀገር ኢትዮጵያ ብዙ ደም የተከፈለባት ለብዙ አፍሪካ ሀገራት የነጻነት ተምሳሌት አለም ፊታቸውን   ወደኢትዮጵያ አድርገው በውስጧ ያሉ ታሪክ ያስቀመጣቸውን ቅርሶቿን   ለመጠቀም ከልጆቿ በተሻለ መልኩ የሚጥሩባት ሀገር ኢትዮጵያ ! አሁን ህዝቧ ሰባዊ መብታቸው እየተደፈረ ባላሰቡት እና ባልጠበቁት መንገድ ወደ ወህኒ ቤት እየተወረወሩ   በህገ መንግስቱ መግደል በስርአት የተደነገገ ይመስል የሰው ሞት የዶሮ ደም የመሰለባት ሀገር! ኢትዮጵያ ! የሰው ልጅ የመናገር መብቱ የታፈነባት   መረጃ በኢንተርኔት የመለዋወጥ መብታቸው በአፍሪካ በአንደኝነት የታፈነባት ሀገር! በሰላማዊ መንገድ ጥያቄ ማንሳትም ሆነ ስለመብት መከራከር እንደወንጀል ተቆጥሮ የባርነት ህይወት ልጆቿ የሚኖሩባት ምድር   ፡በእውነት ያሳዝናል ሰሞኑን ባህርዳር ላይ የተሰሩ ወጣቶችን በአንድም በሌላም መልኩ ማህበረሰባዊ ግዴታችንን በምንወጣበት ሰአት አውቃቸዋለሁ፡፡ ምንም አይነት የስነምግባር ችግር የማይታይባቸውና ከኪሳቸው ገንዘባቸውን አውጥተው የሀገርን ስራ ከሌላቸው ከአፋቸው ቀንሰው የሚሯሯጡ ናቸው አሁንም የታሰሩበት መንገድ በየትኛውም መልኩ ቢሆን የመት ጥሰት ነው የሚመለከታቸው ሲቪክ ማህበራትም ሆነ ሌላው አለም አቀፍ ተቋማት ፈጽመው ሊያወግዙት የሚገባ ነገር ነው ፡፡ ስለዚህ እነዚህ ልጆች በፍጥነት መለቀቅ የለባቸው እና ያለምንም ጥፋት መጎዳት የሌለባቸው መሆኑን ህዝቡ ሊጠይቅና ይፈቱ ዘንድ ከጎናቸው ሊቆም ይገባል https://www.facebook.com/zelalembelayne/?timeline_context_item_type=intro_card_work&timeline...

ስለማንነቱ የሚሞግትን ትውልድ ደንቆሮ ብሎ መሳደብ በሀይማኖታዊውም ሆነ በየትኛውም መንገድ የሀሳብ ልእልና የለውም ከአንድ ትለቅ ሽማግሌ በፐሮፌሰርነት ደረጃ ካለ አዋቂ ነኝ ባይም የሚጠበቅ አይደለም !

Image
ስለማንነቱ የሚሞግትን ትውልድ ደንቆሮ ብሎ መሳደብ በሀይማኖታዊውም ሆነ በየትኛውም መንገድ የሀሳብ ልእልና የለውም ከአንድ ትለቅ ሽማግሌ በፐሮፌሰርነት ደረጃ ካለ አዋቂ ነኝ ባይም የሚጠበቅ አይደለም ! **ዘላለም በላይነህ** ስለማንነቱ የሚሞግትን ትውልድ ደንቆሮ ብሎ መሳደብ በሀይማኖታዊውም ሆነ በየትኛውም መንገድ የሀሳብ ልእልና የለውም ከአንድ ትለቅ ሽማግሌ በፐሮፌሰርነት ደረጃ ካለ አዋቂ ነኝ ባይም የሚጠበቅ አይደለም ! ማቴዎስ አምስት ሃያሁለት እኔ ግን እላችኋለሁ በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ ፍርድ ይገባዋል ወንድሙንም ጨርቃም የሚለው ሁሉ የሸንጎ ፍርድ ይገባዋል ደንቆሮ የሚለውም ሁሉ የገሃነመ እሳት ፍርድ ይጋባዋል፡፡ ይላል ፕሮፌሰር መጀመሪያ ይሄንን ተውልድ ባለጌ እና ደንቆሮ ብለው ከመስደብ ይልቅ በትእግስት እና በእውነተኛው መንገድ ትክክለኛ በሆነ መንገድ ወጣቱን ከስሜታዊነት በጸዳ መልኩ ሀሳብዎን በማስረጃ በመደገፍ ቢያስረዱት የእርስዎንም ክብር ከፍ የሚያደርግ ልዕልና ነበር ፡፡ ስድብን በአውራ ስድብ እየመለሱ እንዴት ከእርስዎ ታላቅነትን ልንማር እንችላን በአንደበቱ ውስጥ ካለው መጥፎ መዝገብ መጥፎ ነገር እያወጡ መናገር ታላቅን ህዝብንም መዝለፍና መድፈር ነውና ይሄ በየትኛወም መንገድ ባለጌነትን እና አላዋቂነትን እንጅ ታላቅንትን አይገልጽም፡፡የወጣቱን የሀሳብ ተቃርኖ ማስረዳት ቢችሉ እና ፕሮፌሰርነትዎን የእውነት መሆኑን ቢያስመሰክሩ ታላቅ እንልዎታለን ፡፡ የጎሳ፣ የብሔር ወይንም የዘውግ ፖለቲካ ለሀገር ጠንቅ መሆኑን ማሳ ምንገድ ቢያጡ አንድን ታላቅ ህዝብ “የለህም” ብሎ ሙግት ውስጥ መግባት ትክክል አይደለም እርስዎ እንዳት (ብልግና ከደንቆሮነት ደንቆሮነት ከብልግና ይወለዳል፤ አነዚህ ሰሞኑን የሚንጫጩት ዱሮ አሳዳጊ የበደላቸው ሲባሉ የነበሩ ዛሬ ...

ፐሮፌሰር መስፍን የንቡረ እድን መዝገብ እንደ ማጣቀሻ ወስዶ አማራ የለም የሚለውን የእልህ አስተሳሰብ ለማጽናት ሲጠቀምበት እና እንደመከራከሪያ ሲያቀርበው እጅግ የአመለካከት ስህተት ብቻ ሳይሆን የአማርኛ ቋንቋም ችግር እንዳለ አስገነዘበኝ! ምክንያም አማራ የለም የሚል ትርጉም ስለማይሰጥ

Image
ፐሮፌሰር መስፍን የንቡረ እድን መዝገብ እንደ ማጣቀሻ ወስዶ አማራ የለም የሚለውን የእልህ አስተሳሰብ ለማጽናት ሲጠቀምበት እና እንደመከራከሪያ ሲያቀርበው እጅግ የአመለካከት ስህተት ብቻ ሳይሆን የአማርኛ ቋንቋም ችግር እንዳለ አስገነዘበኝ! ምክንያም አማራ የለም የሚል ትርጉም ስለማይሰጥ /ዘላለም በላይነህ / 1. አማራ ማለት 1.2. ከሣቴ ብርሃን ተሰማ ‹‹የተመረጠ፣ ነጻነት ያለው ተውልድ፣ … ዐም ሕዝብ፣ ሓራ ሔር የወጣ ጨዋ፣ ነጻነት ያለው ወገን ወይም አሸናፊ፣ ድል ነሺ ዋና አለቃ ማለት ነው፤ 1.3. አለቃ ደስታ ተክለ ወልድ ‹‹ዐም ሕዝብ፣ ሐራ ነጻ በተገናኝ ነጻ ሕዝብ ገዢነት እንጂ ተገዢነት የማይስማርው ማለት ነው፤ ዐማራነት ዐማራ መሆን ተገርዞ፣ ተጠምቆ፣ ማተብ አስሮ የሚኖር ነው፤ 1.4. አለቃ ዓጽሜ አማራ ከወዴትም አልመጣም ጥሩ የላስቶች ወታደር፣ከየዓይነቱ የተጠራቀመ፣ ኃይለኛ፣ ግፈኛ፣ አድመኛ እውቀት ያለው ያልተማረ ጨካኝ ጭፍራ ነው፤ 1.5. የአባ ዮሐንስ ትግርኛ/አምሐርኛ መዝገበ ቃላት ውስጥ አምሐራ ‹‹የኢትዮጵያ ሕዝብ ስም ነው፤›. የሚል ነው፤ 1.6. ንቡረ እድ ኤርምያስ ዐማራ ማለት ‹‹በነጻነት የመኖርን ጸጋ ከእግዚአብሔር በቃል ኪዳን ላገኘው ከየነገዱና ከየጎሣው በጋብቻ፣ በልደትና በኅብረተሰባዊነት ተዋህዶ አንድ ፍጹም ሙሉ ዘር ለሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ የተሰጠ የኅብረ ነገድ ወይም የኅብረ ብሔር አጠቃላይ የባሕርይ መታወቂያ ስያሜ እንጂ የአንድ ጎሣ ስም አይደለም፡፡ ፕ/ር ጌታቸው ኃይሌ እንዳሉት ቃል ያንድ ነገር መጠሪያ ነው። ለምሳሌ፥ “ዛፍ”፣ “ድመት”፣ “ቤት” የምንለው በነዚህ ቃላት የሚጠሩ ነገሮች ቢኖሩ ነው። ባይኖሩ ኖሮ ቃላቱም አይኖሩም ነበር። አንዳንድ ቋንቋዎች ውስጥ ያሉ ቃላት እሌላው ቋንቋ ውስጥ የማይኖሩት በእነዚያ ቃላት የ...
Image
እጼ ሚኒሊክ ለኢትዮጵያ ካበረከቷቸው ወይም የሰሯቸው ድንቅ ስራዎች መካከል..... 1835 ዓ.ም. ---------------------ወፍጮ  1882 ዓ.ም. ---------------------ስልክ  1886 ዓ.ም. ---------------------ፖስታ  1886 ዓ.ም. ---------------------ባህር ዛፍ 1886 ዓ.ም. ---------------------ገንዘብ 1886 ዓ.ም. ---------------------የውሃ ቧንቧ 1887 ዓ.ም. ---------------------ጫማ 1887 ዓ.ም. ---------------------ድር 1887 ዓ.ም. ---------------------የሙዚቃ ት/ቤት 1887 ዓ.ም. ---------------------የፅህፈት መኪና 1889 ዓ.ም. ---------------------ኤሌክትሪክ 1889 ዓ.ም. ---------------------ዘመናዊ ህክምና 1889 ዓ.ም. ---------------------ሲኒማ 1889 ዓ.ም. ---------------------የሙዚቃ ሸክላ 1889 ዓ.ም. ---------------------ቀይ መስቀል 1890 ዓ.ም. ---------------------ሆስፒታል 1893 ዓ.ም. ---------------------ባቡር 1893 ዓ.ም. ---------------------ብስክሌት 1896 ዓ.ም. ---------------------መንገድ 1897 ዓ.ም. ---------------------ፍል ውሃ 1898 ዓ.ም. ---------------------ባንክ 1898 ዓ.ም. ---------------------ሆቴል 1898 ዓ.ም. ---------------------ማተሚያ 1898 ዓ.ም. ---------------------ላስቲክ 1899 ዓ.ም. ---------------------አራዊት ጥበቃ 18...
Image
**የቱ ነው ሰማዕት**** (ዘላለም በላይነህ) ማንነት ሲነካ-- ታሪክ ሲጨፈለቅ-- ያልወደዱት ጀግኖች ሀገር ስትደፈር---- ትኩሱ ደማቸው---- ገነፈለ ወንዶች የተቆጣ ስሜት--- ከፋላ ደም ጋራ---- በአንድነት ቀይጠው ሀውልቱን አቆሙ---- በደም ባጥንታቸው፡፡ የአርበኞቹ ገድል---- አድዋ ያየነው ---- ያሳመመው ፈረንጅ ሊበቀለን መጣ ------በቀሉን ሊወጣ ----ሊገዛን እጅ በእጅ የግራዚያኒ ----መንፈስ ተቆጥቶ--- ሽንፈቱ ሞርሙሮት አእላፍ ገደለ--- በሀበሻ ምድር --- ታሪክ አሳምሞት ባዶዋን ሊያስቀራት ---- ሀገሬን በይፋ አድማሱን ለማስፋት---- መለከት ሲነፋ የእማማ ኢትዮጵያ ----- የቁርጥ ቀን ልጆች በረሀ ሸፈቱ -- እምቢ ላገሬ አሉ---- ተነሱ ደጅ አዝማች  ማንነት ሲነካ--- ታሪክ ሲጨፈለቅ---- ያልወደዱት ጀግኖች ሀገር ስትደፈር--- ትኩሱ ደማቸው------ ገነፈለ ወንዶች፡፡ የተቆጣ ስሜት --ከፋላ ደም ጋራ ---በአንድነት ቀይጠው ሀውልቱን አቆሙ-- በደም ባጥንታቸው፡፡ እንዳሁኑ ትውልድ !!!! በራስ ሜዳ ቆሞ--- ጀግና ነኝ እያለ--- ዘላለም ያይደለ ከገዛ ማንነት ---ከስርአቱ ጋር---- ተጣልቶ በኖረ  ሰማእት እያለ---- ሰማእት ነን ብሎ -- በባዶ ማንነት ---መለከት ነገረ እስኪ መልሱልኝ ሰማእቱ ማነው ? ቂም ያዘለ ፈረንጅ--- በባእድ ማንነት--- ተናዶ ሲመጣ የሰላሳ ሽ ደም ---- በግራዚኒ ---- እንደ ጁስ ሲጠጣ እምቢ ለሀገሬ---ሀገሬ እናቴ ናት ብሎ የሸፈተው  ማቄን እና ጨርቁን----- ዞር ብሎ ያላየው  ወይስ!!! ከወንደሙ ጋራ---- ከአንድ አብራክ በወጣ በዱድም ቢላዋ---- የሰው ደም በጠጣ ? በተጨነቀ ቀን----ችግር በገባበት----- በተራበ ጊዜ ያጎረሰውን እጅ---...
Image
ወይራና ግራዋ - አገርና አድዋ! (DemekeKebede - አድዋ ድልድይ፤ አዲስ አበባ) ( 2007 ዓ.ም) እንደሆነው ቀርቶ - እንዳልሆነው አርገው ቀጥቅጠው፣ በጥብጠው - ቀይጠው ከጠጡት ታሪክ ግራዋ ነው - ከትናጋ አይወርድም - አይችሉም ሊውጡት፤ የሆነውን አምነው - ያልሆነውን ትተው መርገው ሳይሆን ፈልጠው ጠርበው ሳይሆን ጓጉጠው - ታዛ ካስደገፉት ታሪክ ወይራ እንጨት ነው ዘመንና አገርን - ከህዝብ ጎጆ ጋር ሽህ ዕድሜ ያኖራል - የቤት ምሶሶ ነው - አይችሉም ሊጥሉት፤ አድዋም እንዲያ ነው - ግራዋና ወይራ ድልና ሽንፈት ነው - ጣፋጭ ከመራራ፡፡ *** *** *** *** *** ተቀበል አዝማሪ… ‹‹እንዴው ዘ ራ ፌ ዋ… ያልተፃፈ አንባቢ - በሞላበት አገር ታሪክ ያበላሻል - ታሪክን መናገር፤›› ይህንን አዝማሪ… በል ግጠም ይለዋል - የዚህ ዘመን ግጥም ከቶ እንዴት ይቀበል - ታሪክ ሳያጣጥም?! (ከማራራቅ ተምኔት - ከዘር አቡጊዳ እንደ ህያው ጥበብ - ጥላቻ ሲቀዳ በል ያለው ጊዜ ነው - የሆነው ባለዕዳ!) *** *** *** *** *** አዝማሪ ቀጠለ… ‹‹ነይ ነይ ዘ መ ድ ዬ… እልፎች አንድ ሆነው - በሞቱበት አገር ይኸው ነውር ሆኗል - ታሪክን መናገር፤›› ይህንን አዝማሪ.. የሄደ፣ የመጣ - ‹‹ታሪክ›› ተናጋሪ - ሀተታ መንዛሪ ከአገር ታሪክ ላይ - የጎጥ አፅምና - አጥንት ዘርዛሪ ድንገት አመሻሽ ላይ - ጠጪ እንደደከመ - ሰው እንደዛለ አይቶ በል ይለው ጀመረ - ከህዝቦች ታሪክ ላይ - ግለሰብ ለይቶ፤ ይህንን እያየሁ እኔ እንዲህ እላለሁ፤ ‹‹ምኔ ነው አድዋ? ምኔ ነው ሶሎዳ? ምኔ ነው ምኒልክ? ምኔ ናት ጣይቱ? ምኔ ነው አሉላ? ምኔ ነው ዲነግዴ? ምኔ ነው ጎበና? ምኔ ነው ገበየሁ? ምንድኔስ ነው ባልቻ? ለሚል ጥያቄያ...
Image
********አፄ ምኒሊክና ኢትዮጵያ አፄ ምኒሊክና አደዋ ፋኖስና ብርጭቆዎቹ**** (ዘላለም በላይነህ) ነጋሪት እየተጎሰመ ሰራዊቱ እየተመመ ሲሄድ ፈርጠም ባሉ እጆች የእናት አገር ሰንደቅ በክብር መሪነት እየተውለበለበ ወደ ድል ገዞ፡፡ ፍቅርና መስዕዋትነትን ጀግንነትን በቀዩ ቀለም ውስጥ እያነበቡ የምድሩ እሾህ እና ፈለግ ሳይበግራቸው ወደ ምድር አድዋ ሲተሙ ማየት ትክክለኛው ኢትዮጵያዊነት ለመሆኑ ድርጊቱ ያስተምረናል፡፡ እንዳሁኑ ትውልድ ለነገር እንጅ ለተግባር የታነፁ ነዳይ ያይደሉ ይልቁንም ዘር ማንዝሬ ሳይሉ ዳር ድንበርን ለመጠበቅ ጠላትን ለመሞገት ወደ ድል የሞት ሽረት ጉዞ……በምርጡ የቁርጥ ቀን ልጅ በአፄ ምኒሊክ እና ለሀገራችን መከታ እና ማጣበቂያ ጭቃዋ ሁነው ባስዋቧት ባስከበሯት ፣ንፋስ እንዳይገባና መሰረቱ እንዳናጋ መከታ በሆኗት ውድ ልጆቿ ፡፡ ከምድሯ ፍሬ ህይወትን የምንጎነጭባት ከውሆቿም ወተት እየጠባን የምታሳድገን ሀገር ፍቅሯ በአጥንትና ስጋ ገብቶ የማይጠፋ እናት ሀገር ኢትዮጵያ….. ህዝቦቿም በትውልድ በቋንቋ መገናኜት ብቻ ያልተወሰነ የኑሮን ደስታና መከራ ባንድነት በመሮር የተሳሰረ ማንነት የገባቸው ስልፍቅሯ ስለክብሯ ስለታሪኳ ብዙ ሆኑላት ብዙ ተሰውተው ታሪክን ለትውልድ አቆዩ፡፡ የፈረንጅ ውሻ ሊነክሰን ከዘመን ዘመን ሲፈታተነን በውስጣችን እየገባ ሲዘርፈን በልጆቿ ደም እና አትንት ዘበኛነት በእግዚብሄር ረዳትነት ኢትዮጵ ኖራለች እዚህም ደርሳለች፡፡ አለምን የገዛችውን ሮምንም በአፄ ምን ይልክ እና በጣይቱ እራስ ቅልነት ድል አድዋ ላይ ድል ተቀዳጅታለች፡፡ ነፍሳቸውን በገነት በክብር በቸርነቱ ያስቀምጥልን እንጅ ሽዎች ወድቀው ለሚሊዮኖች ቀና ማለት መሰረት ሆነውናል ወደ ድል ጉዞ በባዶ እግር አምስት እና ስድስት ወር ገስግሰዋል ፡፡ ክብር አድዋ ላ...